Duration 31:35

አንጋፋው የሀገራችን የማስታወቂያ አባት ውብሸት ወርቅአለማሁ

61 watched
0
3
Published 2020/03/10

የአንጋፋው የማስታወቂያ ባለሙያ አቶ ውብሸት ወርቃለማሁ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ። የቀብር ስነ ስርዓቱ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመድ፣ የስራ አጋሮቻቸው እና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት ዛሬ 9 ሰዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል። አቶ ወብሸት ባደረባቸው ህመም በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል በህክምና ሲረዱ ቆይተው ባሳለፍነው ቅዳሜ ነበር ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት። በኢትዮጵያ የማስታወቂያ ኢንዱስትሪ ውስጥ ፈር ቀዳጅ የነበሩት አቶ ውብሸት፥ በሃገር ፍቅር ቴአትር ቤት ቴአትሮችን እንዲሁም የቴሌቪዥን ድራማዎችን በመፃፍ እና በመተወን የጥበብ ጎራውን መቀላቀላቸው ይነገራል። በመቀጠልም አንበሳ የተባለ የማስታወቂያ ድርጅት በመክፈት በዘርፉ ሲሰሩ ቆይተዋል። በተጨማሪም አቶ ውብሸት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድን አባል በመሆን ሀገራቸውን በመወከል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማሻሻሉ ረገድ የድርሻቸውን ተወጥተዋል።

Category

Show more

Comments - 0